ሀዲስ አለማየሁ የባህል ጥናት ተቋም 9ኛውን አገር አቀፍ አውደ ጥናት አካሄደ

  • -

ሀዲስ አለማየሁ የባህል ጥናት ተቋም 9ኛውን አገር አቀፍ አውደ ጥናት አካሄደ

Print Friendly, PDF & Email

 

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ (ደ.ማ.ዩ)፣ ሰኔ 6/2014 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) በደብረ ማርቆስ የኒቨርሲቲ የሀዲስ አለማየሁ የባህል ጥናት ተቋም 9ኛውን ሀገር አቀፍ አውደ ጥናት “ባህል ለሰላም እና ለብሔራዊ መግባባት ”በሚል መሪ ሀሳብ ታላላቅ ምሁራን ፣የመንግስት አመራሮች፣ታዋቂ ደራስያን፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ታላላቅ የሚዲያ ባለሙያዎች፣የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲያችን ከፍተኛ አመራሮች ፣ሰራተኞችና ተማሪዎች በተገኙበት በሀዲስ አለማየሁ የጉባኤ አዳራሽ ሰኔ 4 እና 5 በደማቅ ሁኔታ አካሄደ፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is pic2.jpg

በዩኒቨርሲቲያችን የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ መልካሙ በዛብህ (ዶ/ር) በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸው  ባህል በሰዎችና በማህበረሰቦች መካከል መስተጋብር በመፍጠር፣ከሰዎች ጋር እንዴት በሰላም መኖር እንደሚቻል ፣በጋራ ሰርቶ እንዴት  ማደግ እንደሚቻል የሚመራ የአዕምሮ ካርታ ነው፡፡ ይሁን እንጅ ይህን ቱባ ባህል ለሰላም፣ለዕድገትና ለልማት እንዲሁም በፍቅር አብሮ ለመኖር ማድረግ ሲገባን ልጆቻችንን ባለማስተማራችን፣የአንዱን ለአንዱ ባለማሳወቃችን ሀገራችን ሰላም አጥታለች፡፡ በመሆኑም በህዝባችን ዘንድ ተጠብቀው የቆዩትን ዘመን ተሻጋሪ የመቻቻልና የአንድነት እሴቶች በማጎልበት ፣ያለንን ባህል በመጠበቅ ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የአንዱን ባህል ለሌላው ማሳወቅ ከእኛ ይጠበቃል በማለት ገልፀዋል፡፡ በዕለቱ የሚቀርበው ቁልፍ ንግግር እና ጥናት ለባህል፣ ለሰላም፣ ለአብሮነትና ብሔራዊ መግባባት እንዲሆን ተመኝተው እንግዶችን እንኳን ደኅና መጣችሁ ብለዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዝዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው  ባህል የማህበረሰቡን የሞራል ከፍታ በማሳደግ በማህበረሰቡ ዘንድ መልካም ሰብዕና እንዲጎለብት  ብሎም ሀገራዊ እሴቶች እንዲጠበቁ ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ ለዚህም ዩኒቨርሲቲያችን የሞራል ልዕልና ባለቤት እና የመልካም ሰብዕና ተምሳሌት በሆኑት በዕውቁ ደራሲ ክቡር ዶክተር ሀዲስ አለማየሁ ስም የባህል  ጥናት ተቋም በማቋቋም የበርካታ ሊቃውንትና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ስራዎችንም ይዘክራል ብለዋል፡፡ የባህል ተቋሙ ከተቋቋመ ጀምሮ የስነ ፅሁፍ ምሽት በማዘጋጀት የተማሪዎችን የስነ ፅሁፍ ዝንባሌ በማሰደግና መልካም ሰብዕና እንዲገነቡ በማድረግ፣ቤተ መዛግብት በማቋቋም ትልልቅ ማህበራዊ እሴቶች እንዲጎለብቱ ትልቅ ስራ እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ባህል ለኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እድገትም ከፍተኛ ሚና ስላለው ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስፋት ባህል ላይ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is pic3.jpg

የባህል ጥናቱ ተቋም ዳይሬክተር ግዛቸው አንዳርጌ (ረ/ፕሮፌሰር) የባህል ጥናት ተቋሙ የተቋቋመው የኪነ ጥበብ ልማት ስራ ለመስራት፣ ባህልን ለማጥናት፣ ለመሰነድ፣ ለመጠበቅና ለማስተዋወቅ ሲሆን በውስጡ በርካታ ማዕከላትን በማቋቋም ፣ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ፣ ሀገር በቀል እውቀቶችን  በመጠቀም፣ በየወረዳዎች በመዘዋወር የግጭት አፈታትን በማስረፅ  ባህልን ፣ቅርስን ከመጠበቅና ስነፅሁፍን ከመጠበቅ አንፃር በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is pic4.jpg

በመርሀ ግብሩ የደራሲ አበረ አዳሙ አገሬን አፋልጉኝ እና ወንበዴው መነኩሴ የተሰኙ ሁለት መፅሀፍት የተመርቁ ሲሆን ደራሲዉም ከሁለቱም ቅጅዎች ከእያንዳንዱ 25 መፅሀፍት በድምሩ 50 መፅሀፍትን ለዩኒቨርሲቲያችን አበርክተዋል፡፡

ስድስት ባህል ነክ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ እንዲሁም አንኳር ንግግሮች፣ ቅኔ ፣ግጥም፣የማሲንቆና የክራር ጥዑመ ዜማዎችም ቀርበዋል፡፡  

በመጨረሻም የባህል ጥናት ተቋሙ ሊያሻስላቸውና ሊጨምራቸው የሚገቡ ጉዳዮች ዙሪያ በዝርዘር ውይይት ተደርጎ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .