ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች “የህይወት ክህሎት” ስልጠና ተሰጠ

  • -

ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች “የህይወት ክህሎት” ስልጠና ተሰጠ

Print Friendly, PDF & Email

 

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ወጣቶች እና ኤች.አይ.ቪ /ኤድስ መከላከል ዳይሬክቶሬት ያዘጋጀው የህይወት ክህሎት ስልጠና በዩኒቨርሲቲው ለማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ፣ ለስነ-ትምህርትና ስነ-ባህሪ ተቋም እንዲሁም ለቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ሴት ተማሪዎች የተሰጠ ሲሆን ለስልጠና ተሳታፊ ሴት ተማሪዎች እና ለተጋባዥ እንግዶችን  የእንኳን ደህና መጣችህ በማለት ስለ ስልጠናው ገለፃ ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ሴቶች ወጣቶች እና ኤች.አይ.ቪ /ኤድስ መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር  ወ/ሮ ሰላም መክብብ እንዳሉት በዚህ የስልጠና መረሃ ግብር ላይ ዓረዓያ የሆኑ የዩኒቨርሲቲው ሴት መምህራን የህይወት ተሞክሮ እና ፣ የአቻ ግፊትን እንዴት መቋቋም እንደሚቻል ውይይት ይካሄዳል ብለዋል፡፡

በስልጠናው ላይ በመገኘት  በትምህርት ቆይታቸው ያሳለፉትን የህይወት ተሞክሮ ለተማሪዎች ያቀረቡት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የፎክሎር መምህርትና የዩኒቨርሲቲው ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ድርቧ ደበበ (ዶ/ር ) እንዳሉት ተማሪዎች በትምህርት ቆይታችሁ በርካታ ፈተናዎች ሊገጥማችሁ ይችላል፤ ነገር ግን ይህን ፈተና በጥበብና በብልሃት ማለፍ ያስፈልጋል ፣ ይህን ካደረጋችኹ ልታሳኩት የምትፈልጉትን  ዓላማ በቀላሉ ማሳካት ይቻላል ያሉ ሲሆን ወጣትነት ብዙ ነገሮች የሚስተናገዱበት ነው ፤ ሁሉም ነገር በጊዜው ይደርሳል ፤ ጊዜን በአግባቡ መጠቀም በሌላ በኩል ጓደኛን  መምረጥ፣ራስን መሆንና የአቻ ግፊትን መቋቋም አስፈላጊ ነው በማለት ገልጸዋል፡፡  

በመጨረሻም የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡት በዩኒቨርሲቲው የአማረኛ ቋንቋና ስነ-ፅሁፍ ትምህርት ክፍል መምህርትና የስረዓተ ጾታ ተጠሪ ወ/ሮ ሀይማኖት እጅጉ እንደገለጹት ተማሪዎች የቤተሰብ አደራ አለባቹህ ፤ የሃገር አደራ አለባቹህ ስለዚህ ለመጣችሁበት ዓላማ ለራሳቹህ ታማኝ በመሆን ለጥሩ  ውጤት መብቃት ይጠበቅባችኋል  ብለዋል፡፡

በውይይቱ ላይ ሃሳብ ከሰጡት ተማሪዎች መካከል  የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ3ኛ ዓመት ስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት ክፍል ተማሪ ቤተልሔም ማስረሻ እንዳለችው የሴቶች ወጣቶች እና ኤች/አይ/ቪ/ኤድስ መከላከል ዳይሬክቶሬት ስልጠናውን በማዘጋጀት እንድንወያይ፣ እንድንማማር ከሌሎች ዓረዓያ ከሆኑ ሴት መምህራን ተሞክሮ እንድንወስድ  መደረጉ በጣም ጥሩ ነው፡፡ ሴት ተማሪዎችም በሴቶች ክበብ በንቃት መሳተፍ አለባቸው ፤ ስልጠናውና ውይይቱም ቀጣይነት ቢኖረው  በማለት ሃሳቧን ገልጻለች ፡፡

በመርሃ ግብሩ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የትያትርና ጥበባት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች አነቃቂ ድራማዎችን ለታዳሚዎች አቅርበዋል ፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .