በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችና ዲጅታል ቴክኖሎጅ ዙሪያ አውደ ውይይት ተካሄደ

  • -

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችና ዲጅታል ቴክኖሎጅ ዙሪያ አውደ ውይይት ተካሄደ

Print Friendly, PDF & Email

 

የዛሬዋ ዓለማችን በደረሰችበት የእድገት ደረጃ ስልጣኔን ወይም ብልጽግናን ከቴክኖሎጂ ለይቶ ማየት ያስቸግራል። የሰለጠነ ህብረተሰብ ማለት ቴክኖሎጂን ያዳበረ ህብረተሰብ ማለት ነው። ባንጻሩም ቴክኖሎጂን ያላዳበረ ህብረተሰብ ማለት ደግሞ ያልበለጸገ ህብረተሰብ ነው። የሰለጠነ ህብረተሰብ ስንል ደግሞ ድኅነት የተረታበት፤ በሽታ የመነመንበት፤ ትምህርት የተስፋፋበት (እውቀት የለመለመበት)፤ ዲሞክራሲ የሰፈነበት፤ የመገናኛና ቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት በስፋት የተንሰራፋበትና ህግ የበላይ የሆነበት ህብረተሰብ ማለታችን ነው።

ቴክኖሎጂ እላይ ለተጠቀሱት ለሰው ልጆች አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ የሆነ ቀጥተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይሄን ሲይደርግ ግን ቴክኖሎጂ ከህብረተሰብ ውጪ ሆኖ በታዓምር ወይም ትእዛዝ በመስጠት ሳይሆን በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች የሚተገብሩት፤ ሌሎች የህብረተሰብ ምግባራትም ለምሳሌ ትምህርት፤ ኢኮኖሚ፤ ዲሞክራሲ በየፊናቸው ተጽእኖ የሚያደርጉበት ምግባር ነው።

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት የፈጠራ ስራዎች ማበልፀጊያ ማዕከል በማቋቋም በርካታ ስራዎችን በመስራት ላይ ነው፡፡ ዛሬ የካቲት 22/2014ዓ/ም ደብረ        ማርቆስንና  አካባቢውን በቴክኖሎጅ ለማበልጸግና በተለይም ደብረ ማርቆስ ከተማን “High Tech City” ለማድረግ ያለመ አውደ ውይይት ተካሂዷል፡፡

ትምህርት በተግባር የህብረተሰባችን እና የራሳችን ህይወት እንዲቀይር መስራት ይኖርብናል ያሉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) ቴክኖሎጂ ከተጽኖ ነጻ ያልሆነ ቢሆንም፤ እጅግ አስፈሪና አድካሚ የተፈጥሮ ጫናዎችን ያቀለለ፤ የችግሮች መፍቻ ቁልፍና ዘዴም ስለሆነ ተገቢው ትኩረት ከተሰጠው በተጽኖም ስር ሆኖ ህብረተሰባዊ ተልእኮውን መወጣት የሚያስችለው አቅም አለው። ይህም አቅም የሚመነጨው ቴክኖሎጂ ከችግር ፈቺነቱ በተጨማሪ ለፈጣሪው፤ አድራጊው ወይም ከዋኙ ለሆነው ለሰራተኛው ህዝብ አጋዥና ታዛዥ በመሆኑና ከዋኙና አድራጊው ደግሞ አብዛኛው ህዝብ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ለቴክኖሎጅ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት ይደግፋል ብለዋል፡፡

በአውደ ውይይቱ የመነሻ ጽሁፍ ያቀረቡትና በቴክኖሎጅ ዘርፍ ስራ ፈጣሪና የሶፍትዌር አበልፃጊ አቶ ሀብታሙ ቢያዝን  ቴክኖሎጅን መጠቀም የሀገር ውስጥ ችግርን ከመፍታት አልፎ ሶፍትዌርን በማበልፀግ እንደ ማንኛውም ዕቃ ወደ ውጭ በመላክ የገቢ ምንጭ ማድረግ እንደሚቻል አብራርተዋል፡፡ አንዳንዴ የቴክኖሎጅ  ተግባራትን በመፍራት ፣በውጭ ሀገር ብቻ  እንደሚተገበር በማሰብ ራስን ማሳነስ  ሳይሆን በተግባር በመሞከር ውጤታማ መሆን ይቻላል፡፡ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ ጭንቅላትና ኮምፒውተርን በመጠቀም በአጭር ጊዜ በህይወታችን ለውጥ ልናመጣበት የምንችልበት ዘዴ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም ገንዘብ ለማሰባሰብ፣ በበይነ መርብ  አማካኝነት የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን ፣ለተለያዩ የግልም ሆነ የመንግስት ተቋማት ተግባራቸውን ለማቀላጠፍ ያስችላል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የአካውንቲንግና ፋይናንስ መምህር ለጤናህ እጅጉ (ዶ/ር)  አዕምሮ ላይ ያለን ሀሳብ በማፍለቅ ወደ ቢዝነስ ለመቀየር የቢዝነስ ማበልፀጊያ ማዕከል ወሳኝ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ዓለም ከደረሰበት ስልጣኔ ለመድረስ  ማንኛውንም ተግባር ዲጅታላይዝ በማድረግ ቀልጣፋ ተግባርን ማከናወን ይገባል በማለት ዘርፉ ቢዝነስ በመሆኑ ደብረ ማርቆስ እና አካባቢው ከሌላው ዓለም ጋር ሊወዳደርበት የሚችልበትን መልካም አጋጣሚ በመለየት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) ለሀሳቡ ተግባራዊነት በዩኒቨርሲቲ ደራጃ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው በማሳሰብ ዩኒቨርሲቲው የሚሰጣቸው ተቋማዊ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቶች በዲጂታል የተደገፈ ቀልጣፋ አገልግሎቶች በሁሉም የስራ ክፍሎችና ተቋማት መዘርጋት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

በአውደ ውይይቱ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተማሪዎችና መምህራን የተሳተፉ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው የቢዝነስ ማበልፀጊያ ማዕከላትና በማዕከላቱ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ተጎብኝተዋል፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .