በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ እየተከናወኑ የሚገኙ የውስጥ ገቢ ማሳደጊያ ስራዎችና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሄደ

  • -

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ እየተከናወኑ የሚገኙ የውስጥ ገቢ ማሳደጊያ ስራዎችና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሄደ

Print Friendly, PDF & Email

 

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ የሚያከናውናቸው የተለያዩ የልማት ስራዎችና ፕሮጀክቶችን የዩኒቨርሰቲዉ የማኔጅመንት አባላት ፣ የኮሌጅ ዲኖች እና ዳይሬክተሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች እና የአካባቢዉ ማህበረሰብ በተገኙበት መጋቢት 10/2014ዓ.ም የመስክ ጉብኝት ተደርጓል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ታፈረ መላኩ በጉብኝቱ ወቅት እንደተናገሩት ቡሬ ካምፓስ ካለዉ የመልማት አቅም አንጻር በሚፈለገዉ ደረጃ ያልተሰራበት ነገር ግን ጅምሩ የሚበረታታ ስለሆነ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

በዘርፉ ልምድ ካላቸው ዩኒቨርስቲዎች ልምድ በማምጣት በአካባቢዉ ያለዉን የተፈጥሮ ጸጋ በመጠቀም ወደ ስድስት የሚደርሱ በግብርናው ዘርፍ ትኩረት ያደረጉ ፕሮጀክቶችን በዘመናዊ መንገድ በመልማት ላይ መሆናቸውን በጉብኝት ወቅት ተመላክቷል፡፡

ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት ከሆነ እነዚህ ፕሮጀክቶች በቡሬ ካምፓስ ብቻ ሳይወሰኑ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዉ ካምፓሶች ለወደፊት ይተገበራሉ ብለዋል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ ችፍ ኤክስኪቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ብርሃኑ ዓለሙ እንደገለጹት ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ አመራሮች እንዲሁም ሁሉም አካላት በመተባበር ከዩኒቨርሰቲ ከፍተኛ አመራሮች በተቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን የካምፓሱን የዉስጥ ገቢ በማሳደግና አካባቢዉን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የዶሮ እርባታ፣ የንብ ማነብ፣ የበጋ መስኖ ልማት፣ ለስጋና ሌሎች ተግባራት የሚውሉ ከብቶች ማድለብ፣ ሰው ሰራሽ ሀይቅ በመፍጠር የዝናብ ውሃን መገደብ የተለያዩ አትክልቶችና ፍራፍሬ እንዲሁም የሻይ ቅጠል ምርትን በዘመናዊ ዘዴ የማልማት ስራ የታሰቡ ፕሮጀክቶች እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሰቲ ቡሬ ካምፓስ አካዳሚክ ጉዳዪች ዳይሬክተር አቶ ዉባለም ጎቤ በበኩላቸዉ የዛሬዉ ጉብኝት ዓላማዉ በከፍተኛ አመራሩ ድጋፍ ካምፓሱ ዉስጥ እየለሙ ያሉ ልማቶችን ለማሳየት እተደረገ ጉብኝት እንደሆነና ለወደፊት ታቅደዉ በካምፓሱ ወስጥ ለሚሰሩ ልማቶችን ግብዓት በመቀበል በቀጣይነት አጠናክሮ በመቀጠል ሌሎች ለዩኒቨርሲቲዉና ለካምፓሱ ገቢ ማመንጫ የሚሆኑ የልማት ስራዎችን ለማከናወን ዝግጅት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል፡፡

ከመሰክ ጉብኝቱ መልስ አጭር ግብረ መልስና ውይይትም ተካሂዷል፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .