“አድዋ የኢትዮጵያ የዘመናት የድል ብስራት ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ሃውልት ጭምር ነው፡፡ ሆኖም በተለያዩ ዘርፎች ሪከርዶች ይሰበራሉ በጦርነት ድል ግን የአድዋን ድል ሪከርድ ማንም ሊሰብረው አይችልም፡፡” ዶ/ር ታፈረ መላኩ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት

  • -

“አድዋ የኢትዮጵያ የዘመናት የድል ብስራት ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ሃውልት ጭምር ነው፡፡ ሆኖም በተለያዩ ዘርፎች ሪከርዶች ይሰበራሉ በጦርነት ድል ግን የአድዋን ድል ሪከርድ ማንም ሊሰብረው አይችልም፡፡” ዶ/ር ታፈረ መላኩ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት

Print Friendly, PDF & Email

 

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ 126ኛውን የአድዋ ድል በዓል ‹‹አድዋ ለኢትዮጵያውያን ህብረት ለአፍሪካውያን የነጻነት ጮራ ›› በሚል መሪ መልዕክት በንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የሐዲስ ዓለማየሁ የጉባዔ አዳራሽ በፓናል ውይይት ተክብሯል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ  የኢትዮጵያ የዘመናት የድል ብስራት ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ሃውልት ጭምር ነው፡፡ ሆኖም በአትሌቲክሱ ዘርፍም ሆነ በሌሎች ዘርፎች  ሪከርዶች ይሰባበራሉ በአትሌቲክሱ  የአንዱን አትሌት ሌላኛው ወስዶታል የተመዘገበውን ውጤትም ሲያሻሽለው ተመልክተናል ያሉት ፕሬዚዳንቱ  በጦርነት ድል ግን በዛ በማይመጣጠነው በአውሮፕላን መርዝ እየረጨ መድፍና ታንክ እያጓራ በቁመህ ጠብቀኝ በጋሻና ጦር ያንን ዘመናዊ የነጭ ወራሪ በስድስት ሰዓት ውስጥ ያሸነፈው ጥቁር ህዝብ ነው፡፡ የአድዋ ድል በየትኛውም ዘመን በጦርነት ድል ሪከርድ የማይሰበርበት  ድል ነው በዚህም ኩራት ይሰማናል፡፡ ለአባቶቻችን ለኢትዮጵያውያን ክብር ይገባል፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያውያን ከአራቱም ማዕዘን ከሰሜን፣ ከደቡብ፣ ከምስራቅ፣ ከምዕራብ ከየአካባቢው ከጎጃም ፣ከሸዋ ፣ ከሀረር ከእያንዳንዱ አካባቢ ተጠራርቶ ዘረኝነት የለ ሁሉም ለአንድ አላማ ለሃገር ፍቅር ለሀገር ክብር በመዋደቃቸው በስድስት ሰዓት ውስጥ በማይታመን መንገድ ማሸነፍ ተችሏል፡፡ ይሁን እንጅ ዛሬ ከአድዋ መማር የምንችለው  ፍቅር፣ ወንድማማችነት፣ፍጹም ኢትዮጵያዊ መሆን ይህ ሀገር ለማሳደግ፣ ሀገርን ወደ ወሳኝ መንገድ ለመውሰድ ትልቅ ስንቅ ሆኖ ያሉ ሲሆን ሌላው በተለይ ወጣቱ ትውልድ ከአድዋ የሚማረው ነገር ቢኖር አንደኛው ፍጹም ኢትዮጵያዊነትን መገንባት ሁልጊዜ የኢትዮጵያዊነት መንፈስ በልቦናው ውቅር ውስጥ እንዲጎመራ ምንጊዜም መትጋት፡፡ ሁለተኛው የሀገር ፍቅር እስከ መስዋትነት ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሐዲስ ዓለማየሁ የባህል ጥናት ተቋም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተርና የታሪክ መምህር  አቶ ግዛቸው አንዳርጌ (ረ/ፕ) “የኢትዮጵያ ህልውና እና የውጭ ጣልቃ ገብነት አድዋ እንደ ማሳያ” በሚል ርዕስ ለውይይት ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን  ሌላኛው የታሪክ መምህር  አየነው ማሞ (ዶ/ር)  “ለአድዋ ድል የአጼ ሚኒሊክ እና የእቴጌ ጣይቱ ሚና እና ለወጣቱ ያለው አስተምህሮ” በሚል ርዕስ  ጽሁፍ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በድል በዓል አከባበሩ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና በደብረ ማርቆስ ከተማ ወጣት ከያኒያን የተለያዩ ኪነ-ጥበባዊ ስራዎች ለታዳሚዎች ቀርበው የአድዋን መንፈስ በመዘከር አስታውሰዋል፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .