ዓለማዊ ትምህርትና የኢትዮጵያዊያን ማያ መስተጋብር በሚል አውደ ውይይት ተካሄደ

  • -

ዓለማዊ ትምህርትና የኢትዮጵያዊያን ማያ መስተጋብር በሚል አውደ ውይይት ተካሄደ

Print Friendly, PDF & Email

 

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ “ዓላማዊ ትምህርትና የኢትዮጵዊያን ማያ መስተጋብር” በሚል ርዕሰ ጉዳይ አውደ ውይይት የተካሄደ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው መምህራንና ሰራተኞች እንዲሁም ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡ በአውደ ወይይቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተወካይና የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ይሄይስ አረጉ (ዶ/ር) ዛሬ ለውይይት የተመረጠው ርዕሰ ጉዳይ የትምህርት ተቋማት በየዓመቱ የሚያስመርቋቸው ወጣቶችና በትምህርት ተቋማት የሚገኘው ማህበረሰብ ዓለማዊ ትምህርትን ከኢትዮጵያ እሴትና ባህል አኳያ እንዴት እንደሚቃኝ እንዲሁም እንደ ሃገር ዓለማዊ የትምህርት ስርዓታችን ያፈራው ትውልድ ከኢትዮጵያዊነት ባህልና እሴት ያለውን ተዛምዶ ማያ ልናደርገው የሚገባ  ውይይት ይሆናል ብለዋል፡፡  “ዓላማዊ ትምህርትና የኢትዮጵዊያን ማያ መስተጋብር” በሚል ርዕሰ ጉዳይ የውይይት መነሻ ፅሑፍ በወጣቶች ስነ-ምግባር ዙሪያ እና በግጭት አፈታት ዙሪያ አማካሪ የሆኑት ዓለም አቀፍ ምሑር አቶ ፈንታሁን ዋቄ ያቀረቡ ሲሆን በፅሑፋቸው ስድስት ያክል ጥያቄዎችን በማንሳት ተሳታፊዎችን ሞግተዋል ። ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከልም የኢትዮጵያ ዓለማዊ ትምህርት ስርዓትና ይዘት የሚመራበት ፍልስፍና ከየት አገኘው ? የማን ነው ? ለሰው ልጆች ማንነትና ለዓለም ያለው ርዕይ ምንድን ነው ?  እንዲሁም በተውሶና በሙከራ እውቀትና ርዕዮት አገርን አገር አድርጎ ማቆም ይቻላል ? የሚሉት ይገኙበታል፡፡

አቅራቢው አቶ ፈንታሁን ዋቄ የዘመኑን የማድነቅ ሳይሆን የሚቆነጥጥ አሉታዊ ወቀሳ ያለበት፤ ከምንገኝበት ምቾት በመውጣት ፅኑና ጥልቅ ጥያቄዎች በራሳችን ላይ ማንሳት ይኖርብናል በማለት ንጥል-ግንጥል የሆነ ዕይታ ሳይሆን ሁሉንም ማዕከል ያደረገ ተዋህዷዊ ዕይታን በማዳበር ግንዛቤና ህሊናን የሚያከበር ሁኔታን ለትውልዱ መፍጠር ይኖርብናል ያሉ ሲሆን ውጭን ብቻ የሚመለከት ምሑራዊነት ለአገራዊ ውድቀት ዋና መንስኤ በመሆኑ ወደ እራሳችን በመመለስ ታሪካዊና ባህላዊ እሴቶቻችን ለሀገር ግንባታ መጠቀም ይኖርብናል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም በውይይቱ ከተሳታፊዎች የተለያዩ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል ፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .