የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የግብርና መሳሪያዎችን በማስገባት የአካባቢውን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ነው

  • -

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የግብርና መሳሪያዎችን በማስገባት የአካባቢውን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ነው

Print Friendly, PDF & Email

 

የአገራችን የግብርና ዘርፍ ባለፉት ዓመታት ችግሮችን የመቋቋም አቅም የገነባ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በመንሸራትት ላይ መሆኑ በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ የመቋቋም አቅም ገንብቷል የሚያሰኘው ለዘመናት ባልተቀየረ የማረሻ መሳሪያና የአስተራረስ ስልት በማደግ ላይ ያለውን የአገሪቱን ሕዝብ ቁጥር የመመገብ ግዴታውን በመወጣት ላይ መሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከ10 ሽህ ዓመታት በፊት በኒዮሊቲክ አብዮት ዘመን ጀምሮ የበርካታ የአዝእርትና እንስሳት ሀብት መፍለቂያ ነች፡፡ ከዚያን ዘመን ጀምሮ የአገራችን ገበሬ በትግበራ ያካበተውንና በተፈጥሮ የተሰጠውን ችሎታ በመጠቀም በዘመናዊና ቴክኖሎጂ ወለድ በሆኑ መሳሪያዎች ሳይታገዝ፣ በአንድ በኩል በየጊዜው የአፈሩ ለምነት እየቀነሰ በሌላ በኩል ቁጥሩ እየናረ የሚሄደውን ህብረተሰብ በመመገብ ላይ ይገኛል፡፡ ይህንንም ግዴታ ለመወጣት አርሶ አደሮች በሚያደርጉት የእርሻ መሬት ማስፋፋት የተፈጥሮ ሀብትን መመናመንና የስነ-ምህዳር መዛባትን በማያስከትሉ በዘላቂ ህልውናቸው ላይ አደጋን ሊጋብዙ ችለዋል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሰብል ልማትና የግብርና ምርቶች ማቀነባበር ዘርፍ  የግብርናውን ዘርፍ በምርምር በመደገፍ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ይገኛል፡፡ በያዝነው ዓመትም  የአካባቢውን አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደ አገር ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ማህበረሰቡ ለከፋ ረሀብና ችግር እንዳይገለጥ ለማድረግ  በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤሊያስ ወረዳ የግዳድ ቀበሌ 255 ሄክታር እንዲሁም በማቻከል ወረዳ ከ48 ሄክታር መሬት በላይ  አስፈላጊውን ግባዓትና በማሟላት የበጋ መስኖ ስንዴን እያለማ ይገኛል ፡፡ ይህንን የበለጠ ለማሳደግና አርሶ አደሩን የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድርግ እየሰራ የሚገኘው ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ዘመናዊ የግብረና መሳሪያዎችን መግዛቱን አስታውቋል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር እሱባለው መኩ እንደገለፁት አካባቢው ከፍተኛ የሆነ የግብርና ስራ የሚከናወንበት ስለሆነና  አብዛኛውን የሀገሪቱ ምርት የሚመረትበት አካባቢ እንደመሆኑ መጠን የግብርና ስራው ግን ባለመዘመኑ የተነሳ በሚፈለገው መጠን ምርት እየተመረተ አይደለም  በዚህም የተነሳ ዩኒቨርሲቲው የራሱን ድርሻ ለመወጣት የግብርና መካናይዜሽኑን ሊደግፍ የሚችል አራት የተለያየ የፈረስ ጉልበት ያላቸው  የእርሻ  ትራክተሮችና  አንድ ኮምባይነር  በ37 ሚሊየን ብር  ግዥ በመፈፀም አርሶ አደሮችን በኩታ ገጠም እርሻ ስራ ተጠቃሚ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑን የገለጹ ሲሆን መሳሪያዎቹ ለምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ከፍተኛ አስተዋፅኦ አላቸው ብለዋል፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .