Monthly Archives: May 2021

  • -

ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ግቢ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ፓሊሲና ስትራቴጂ፣ የአስር ዓመት መሪ የልማት ዕቅድና ቁልፍ የዉጤት አመላካቾች ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ

ደ/ማ/ዩ (መጋቢት፣ 2013 ዓ.ም)፡- በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ፓሊሲና ስትራቴጂ፣ የአስር ዓመት መሪ የልማት ዕቅድና ቁልፍ የዉጤት አመላካቾች “የጠራ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ፓሊሲ፣ ስትራቴጂ፣ የልማት ዕቅድና ፕሮግራሞች ለሁለንተናዊና ዘላቂ ሀገራዊ እድገት” በሚል መሪ ቃል ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ መጋቢት 13/07/2013ዓ.ም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

በዕለቱም የስልጠናዉ ዓላማ እና አካሄድ ላይ አጭር ገለጻ ከተደረገ በኋላ በከፍተኛ ትምህርት ፓሊሲና ስትራቴጂዎች፣ የሳይንስና ፖሊሲ ስትራቴጂዎች፣ የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስ ልማት የአስር ዓመት መሪ ዕቅድ እና ቁልፍ አመላካቾችና የደብረ ማርቆስ የኒቨርሲቲ የአምስት አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ የሚሉ ሰነዶችን የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲተ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚደንት ዶክተር ይሄይስ አረጉና የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ምክትል ፕሬዚደንት ዶክተር ሞላልኝ ታምሩ አቅርበዋል፡፡

ስቀረቡት  ሰነዶችና  ስለ ዉይይቱ አጠቃላይ ይዘት የቡሬ ግቢ ዲን  ዶክተር ጸበሉ አባይነህን አናግረናቸዉ የሚከተለዉን ምላሽ ሰጥተውናል፡፡ ስልጠናዉ በከፍተኛ ትምህርት እና በሳይንስ ልማት በተያያዘ በተደራሽነት፣ በጥራት፣ አግባብነትና ፍትሐዊነት የተሰሩ ሰራዎች ሀገሪቱ መመለስ ካለባት ጥያቄዎች አንጻር ጎላ ያሉ ክፍተቶች እንዲሁም ከመሰረተ ልማት ጋር የተየያዙ ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች ተነስተዋል፡፡

በተጨማሪም  በስልጠናዉ እንደ ትልቅ ነጥብ ሆኖ የተነሳዉ ለራስ ትኩረት በመስጠት በሀገር በቀል እዉቀትና በፈጠራ ስራ ላይ  እየተሰራ ያለዉ ስራ በአፈጻጸም ደረጃ ዝቅተኛ በመሆኑ የራስን ችግር ለመፍታት ማነቆ እንደሆኑ በሌላ በኩል ደግሞ ከበፊት ያልተፈጸሙ ፓሊሲዎችና ስትራቴጂዎች አሁን ላይ ተግዳሮት እንደሆኑ፤ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ትምህርት የሳይንስና ልማት የአስር ዓመታት መሪ ዕቅድና ቁልፍ የዉጤት አመላካቾች መሰረት ያደረገ  የአምስት አመት ስትራቴጂ ዕቅድ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንን፤ ከዚህም በመነሳት የቡሬ ግቢ የራሱን ዕቅድና ስትራቴጂ ማዘጋጀቱ ተገልጧል፡፡

 በመጨረሻም ስልጠናዉ ሁሉም ፈጻሚ አካላት እንደ አንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ሰራተኞች የከፍተኛ ትምህርት ፓሊሲዎችና ስትራቴጂዎች የወደፊት የልማት ዕቅዶች ላይ የጠራ ግንዛቤ ፈጥሮላቸዋል የሚል እምነት እንዳላቸዉ  በመግለጽ ሃሳባቸዉን አጠቃለዋል፡፡



  • -

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ ሁለተኛውን አመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባኤ በደማቅ ሁኔታ አካሄደ

 

ደ/ማ/ዩ፡-ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ ሁለተኛውን አመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባኤ “የተቀናጀ የእሴት ሰንሰለት ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ቃል ጥሪ የተደረገላቸው እንግደች፣ ተመራማሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣የአካባቢው ነዋሪዎችና የካምፓሱ ማህበረሰብ በተገኙበት በቡሬ ካምፓስ ከግንቦት 14-15/2013 ዓ.ም  በደማቅ ሁኔታ አካሂዷል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዘዳንት ረዳት ፕሮፌሰር ሲስተር ገነት ደጉ በጉባኤው መክፈቻ ንግግራቸዉ ደብረ ማርቆስ የኒቨርሲቲ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ላይ የትኩረት አቅጣጫውን አድርጎ ለአካባቢው ማህበረሰብ ችግር ፈች የሆኑ ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ ለማህበረሰቡ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

               የጉባኤዉ ከፊል ገጽታ

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቡሬ ካምፓስ ዲን ዶክተር ጸበሉ አባይነህ በበኩላቸው በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው በ2006 ዓ/ም ካምፓሱ በመደበኛው የመጀመሪያ ዲግሪ መርሃ-ግብር በአራት የትምህርት መስኮች 175 ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር የጀመረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ካምፓሱ አንድ ዲን፣ አምስት ምክትል ዲኖች፣ አሰራ አራት ኦፊሰሮች እና አስራ ሁለት ትምህርት ክፍሎች እንዳሉት ገልጸው ካምፓሱ የተጠናቀቁና በመሰራት ላይ ያሉ የማስፋፊያ ግንባታዎችን በመጨረስ በቀጣይ የቅበላ አቅሙን የበለጠ በማሳደግ የመማር-ማስተማር ሂደቱን ለማሳለጥ  እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የጉባኤው  ቁልፍ ንግግር አድራጊ በጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አበባው ጋሻው በንግግራቸዉ “የአንድ ሀገርን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ በእዉቀት ላይ የተመሰረተ ጥናትና ምርምር ላይ ትኩረት አድረጎ መሰራት አስፈላጊ ነው” ብለዋል፡፡

ለሁለት ቀናት የቆየው የምርምር ጉባኤ በሶስት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን እነሱም ግብርና ተፈጥሮ ሃብት፤ ስነ-ምግባር፣ ሰላምና ፆታዊ ተሳትፎ  እና ቢዝነስና ኢኮኖሚ ሲሆኑ በአጠቃላይ 28 ጥናትና ምርምር ስራዎች በአጥኝዎች ቀርበው ተሳታፊዎች ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን ሰጥተውባቸዋል፡፡ ከእዚህ ጋር ተያይዞ በአውደ ጥናቱ የቀረቡት የጥናትና ምርምር ስራዎች ከወረቀትነት አልፈው ወደ መሬት ወርደው የማህበረሰቡን ችግር ፈች ሊሆኑ ይገባል ተብሏል፡፡

በመጨረሻም በቡሬ ከተማ የተገነባው ፌቪላ የምግብ ዘይት ማምረቻ ኮምፕሌክስ ፋብሪካና  በካምፓሱ የተጠናቀቁና በመሰራት ላይ ያሉ የማስፋፊያ ግንባታዎች ጉብኝት ከተካሄደ በኋላ ለጥናትና ምርምር አቅራቢዎችና ለክብር እንግዶች የእዉቅናና የምስጋና የምስከር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡


  • -

Debre Markos University Burie Campus to host the Annual National Research Symposium colorfully

Debre Markos University Burie Campus to host the 2nd Annual National Research Symposium colorfully with the theme “ Integrative Research Through Value Chain for Sustainable Development” in the presence of higher government officials, scholars, researchers, religious fathers, dwellers of the town and Burie Campus community from May 22-23, 2021.


DMU Radio Broadcasting . . .