የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሕንፃ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

  • -

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሕንፃ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

 

በዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት ዶክተር ቴዎድሮስ በካፋ ስም የተሰየመው ይህ ግዙፍ ሕንፃ በዩኒቨርስቲው ዋና ግቢ ከተገነቡ ትላልቅ ህንፃዎች አንዱ ሲሆን  ህንፃው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የዩኒቨርሲቲያችን ሰራተኞች ያለባቸዉን የቢሮ ችግር ከመቅረፉ ባሻገር ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር የአገልግሎት አሰጣጡን ያሻሽላል ተብሎ ይታመናል፡፡

የሕንፃው ግንባታ ሰኔ 18 ቀን 2007 ዓ.ም ውል ተይዞ የተጀመረ ቢሆንም በግንባታ ስራ ተቋራጮች ደካማ የስራ አፈፃፀም፣ በግንባታ ግብዓቶች ዋጋ መናር እና በሌሎችም የተለያዩ  ምክንያቶች መጠናቀቅ ከነበረበት ጊዜ ዘግይቶ ተጠናቋል፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is Building-2-1.jpg

የቴዎድሮስ በካፋ ሕንፃ ግንባታ ስራ ተደጋጋሚ የዉል ማቋረጥ ገጥሞት ነበር፡፡ ይሁን እንጅ በዩኒቨርሲቲያችን ማኔጅመንት የቅርብ ክትትልና ጠንካራ ዉሳኔ ተሰጥቶ ከፌደራል ግዥ ኤጀንሲ በማስፈቀድ በደብረ ማርቆስ ከተማ ለሚገኘውና የመንግስት የልማት ድርጅት ለሆነዉ መንቆረር ኮንስትራክሽን ድርጅት ተሰጥቶ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ቀሪ የግንባታ ሂደቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት በቅቷል። በዚህ አጋጣሚም የመንቆረር ኮንስትራክሽን ድርጅት ላሳየው የስራ ጥራትና ቅልጥፍና ማመስገን እንወዳለን።


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .