Category Archives: News

  • -

የደብረ ማርቆስ  ዩኒቨርሲቲ  4ኛውን  ዙር  የተማሪዎች  አምባሳደር  የእውቅናና ሽልማት መርሐ ግብር አካሄደ

 

ዩኒቨርሲቲያችን ከተመሰረተ ጀምሮ በርካታ ተማሪዎችን በማሰልጠን ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ግልጋሎቶች የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ  ይገኛል። ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለመፍጠር አልሞ እየሰራ ያለው ዩኒቨርሲቲያችን የመማር ማስተማር ስራውን የተሳካ ለማድረግ ልዩ ልዩ ተግባራትን እያከናወነም ይገኛል።

በተማሪዎች ውስጥ የተወዳዳሪነት መንፈስን በመፍጠር በትምህርታቸው ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ በማሰብ ዩኒቨርሲቲው ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመመልመል የእውቅናና ሽልማት መርሐ ግብር እያዘጋጀ ለተማሪዎች በአምባሳደርነት የክብር ማዕረግና ሽልማት እየሰጠ ይገኛል።

የ2015 ዓ.ም የ4ኛው ዙር የተማሪዎች የአምባሳደር  የእውቅናና ሽልማት መርሐ ግብርም መጋቢት 16 እና 17 ቀን /2015 ዓ.ም የፌደራል መንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ ዲኖች ፣ ዳይሬክተሮች ፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በተገኙበት በዋናው ግቢ እና በቡሬ ካምፓስ በደማቅ ሁኔታ ተካሄዷል።

This image has an empty alt attribute; its file name is Ambassador-2.jpg

በዚህ የሽልማትና የእውቅና መረሐ ግብር  ላይ ተገኝተው ለተሸላሚ ተማሪዎች መልዕክት ያስተላለፉት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ.ር ይኼይስ አረጉ እንደገለፁት በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ ያሳለፍናቸው አያሌ ዘመናት እውነታ እንደሚያመለክተው በየጊዜው የነበረው ትውልድ ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታው ያቀረበለትን ገፀ በረከቶች እየተጠቀመና የሚችለውን ያህል በማደረግ ታሪካዊ ግዴታውን እየተወጣ፤ ቀደም ሲል ያልተመለሱ ጥያቄዎችንና ያልተፈቱ ችግሮችን ደግሞ እየመለሰ፣ እየፈታና እያቃለለ እንዲሁም የታሪክ ቅብብሎሹን እያሳለጠ እንደመጣ ይታመናል ያሉት ዶክተር ይሄይስ ይህ የሚያሳየው ደግሞ የየዘመኑ ትውልድ ከቀደሙ አባቶች ወይም ከሚኖርበት ዓለም የሚቀርብለት ወርቃማ ዕድል እንዳለ ሁሉ የሚጋፈጠው ዕልህ አስጨራሽ ውድድርና ትግልም የሚጠብቀው መሆኑን ነው፡፡

ከዚህ አንፃር በአፅናፉዊ ትስስር የፍልስፍና ማዕቀፍ እየተመራ ያለው አሁን የምንኖርበት የ21ኛዉ ክፍለ ዘመን የሁኔታዎች ተለዋዋጭነት የበዛበት፣ ከፍተኛ ስጋትና ጥርጣሬ የነገሰበት፣ ለውጥ የፈጠነበት፣ የሰው ልጅ ፍላጐት ከጊዜ ጊዜ እየተውሰበሰበ የመጣበት፣ ሳይንስና ዲጂታል ቴክኖሎጂ እየረቀቀና እየመጠቀ የመጣበት እንዲሁም ውድድር የከረረበት እንደሆነም ጠቅሰዋል፡፡

ለዘመናት በተፈጥሮ ላይ ተንጠልጥሎ የቆየው የሰው ልጆች የአኗኗር ሁኔታም የሳይንሳዊ ዕውቀትን ድጋፍ የጠየቀበት ዘመን ላይ የምንገኝ መሆኑንም መገንዘብ እንደሚገባም ያስገነዘቡት ም/ፕሬዚደንቱ  በእንደዚህ ዓይነት ፍፁም ተገማች ያልሆነ ዓለም ውስጥ የሚኖርና ለስኬት፣ ለጥሩ ውጤትና ለተሻለ ተጠቃሚነት የሚተጋ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ማህበረሰብ ያስቀመጠውን ራዕይ በተፈለገው ደረጃ ለማሳካት ይችል ዘንድ የአስተሳሰብም ሆነ የአሰላለፍ ቅኝቱ ሁልጊዜም በተፎካካሪነት መንፈስና በሳይንሳዊ ዕወቀት፤ በጥበብና በማስተዋል ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ይታመናልም ሲሉ ገልፀዋል፡፡

አሁን ትምህርቱን በመከታተል ላይ ያለው ወጣቱ ትውልድ ከላይ የተዘረዘሩትን ወሳኝ የዘመን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል ሳይንሳዊ፣ ስነ ልቦናዊና አካላዊ ዝግጁነት እንዲኖረው አድርጐ ማስተማር ፣ መምከር ፣ ማበረታታትና ማብቃት እንዲሁም የተለየ ጥረትና ትጋት ለሚያሳዩና አብላጫ ወጤት ለሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ዕውቅና መስጠት የትምህርት ተቋማት ታሪካዊ ሃላፊነት መሆኑን መገንዘብና መተግበር ለሃገርም ለትውልድም አሰተወጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም በአፅንኦት ገልፀዋል።

ይህን ጉዳይ በጊዜ የተረዳው የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎቹን የተፎካካሪነትና የተወዳዳሪነት ስሜት ከፍ ለማድረግና አቅማቸውን አሟጠው ለትምህርታቸው ብቻ እንዲጠቀሙና ውጤታማ እንዲሆኑ ለማድረግ ባለው ፍፁም ዕምነትና ቁርጠኝነት በየዓመቱ በአጠቃላይ 3.75ና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እንዲህ በደመቀ ሁኔታ በፕሬዝደንት አምባሳደርነት ማዕረግ ዕውቅና በመስጠት፣ በመሸለምና በማበረታታት ረገድ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቸኛው ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መሆኑን ስንገለፅ ታላቅ ክብር ይሰማናልም ሲሉ አክለዋል።

ዛሬ ዕውቅና የምንሰጣቸው ጀግና ፣ ታታሪና አሸናፊ ተማሪዎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም በጠንካራ የውድድር ስሜትና ታላቅ ተስፋ ታጅበው ሲማሩ፣ሲያጠኑና በትምህርታቸው ሲበረቱ የቆዩ በመሆናቸው ባስመዘገቡት አብላጫ ውጤት ምክንያት በመሆኑ እነዚህ ባለሙሉ ተስፋ ልጆች ከራሳቸው የመንፈስ እርካታ በላይ ያሳደጓቸው ቤተሰቦችና ያስተማሯቸው መምህራን የሚሰማቸው ክብርና ኩራት በቀላሉ የሚገመት አይሆንም፡፡

በመጨረሻም ባለፉት ተከታታይ ሴሚሰተሮች የትምህርት ጊዜያችሁን በአግባቡ በመጠቀማችሁ፣ የተሸለ ጥረት በማድረጋችሁና ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገባችሁ ዛሬ ዕውቅናና ሽልማት ስትቀበሉ ቀጣዩን የመማር ጉዞ ከዛሬው በላቀ ወጤት ለመዝለቅ ሞራልና ወኔ እያገኛችሁና ወደፊት ለመንደርደር የሚያሰችላችሁን ጉልበት እያጠራቀማችሁ መሆኑን በመተማመንና ወደፊት በሚጠብቃችሁ ዲጂታል ውድድር ውስጥ ድልን በመቀዳጀት መሆን የምትፈልጉት ጫፍ ላይ እንደምትደርሱ እርግጠኛ በመሆን ቀሪ የትምህርት ጊዜያችሁና አጠቃላይ ህይወታችሁ ስኬታማና ዉጤታማ እንዲሆን ከልብ በመመኘት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is Ambassador3.jpg

በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለተማሪዎች መልዕክት ያስተላለፉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ- ልቦና መምህርትና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት  ማስተዋል መኮንን (ዶ.ር ) እንደገለጹት በዚህ የተማሪዎች የሽልማትና ዕውቅና ፕሮግራም ላይ ተገኝተው ሀሳባቸውን እንዲያካፍሉ በመጋበዛችው ዩኒቨርሲቲውን አመስግነው ተማሪዎችም በወጣትነት ጊዜ በርካታ ፈተናዎችና ውጣውረዶች እንደሚያጋጥማቸው ገልጸው ተማሪዎች ይህንን ትግል አሸንፈው ለዚህ ውጤት በመብቃታቸው  ሊኮሩ እንደሚገባቸው ጠቅሰው ነገሮችን በሰከነ አዕምሮ ዓላማቸውን ማሳካት እንዳለባቸው በቀጣይም ይህንን ጥንካሬ የበለጠ ማስቀጠል እንዳለባቸው እና የራሳቸውንም ተሞክሮዎች በማንሳት ለተማሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is Ambassador4.jpg

በዚህ ፕሮግራም ላይ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ እውቅናና ሽልማት ከተደረገላቸው ተማሪዎች  መካከል ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ትዕግስት ታረቀኝ 3.96፣ ብሩክ አወቀ 4፡00 እና ደረጀ ወርቄ 4፡00 በማስመዝገብ ዘመናዊ ታብሌት ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ሽልማቱም በትምህርታችን ላይ ትኩረት እንድናደርግ ያነሳሳናል ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው እንዲህ ዓይነት ፕሮግራም በማዘጋጀት ለተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ማድረጉ ለአዲስ ገቢ ተማሪዎችም መነቃቃትን፣ መነሳሳትን ይፈጥራልና ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ሲሉም አክለዋል። በርካታ ጫናዎችና ፈተናዎች ቢኖሩም እንኳ የአላማ ጽናትና ጥንካሬ ካለ ዓላማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ገልጸዋል። ይህ ውጤትም የቤተሰቦቻቸው ፣ የመምህሮቻቸው እና የጓደኞቻቸው ውጤት እንደሆነ ፤ በእነሱ ድጋፍና ጥረትም ለዚህ በቅተናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡


  • -

ከእንሰት ምርት የተዘጋጀው ምግብ እንዳስደሰታቸው በወንቃ ቀበሌ የሚገኙ አርሶ አደሮች ተናገሩ

 

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በመተባበር በአማራ ክልል እንሰትን ለምግብነት የማላመድ ፕሮጀክት በምስራቅ ጎጃም ዞን በአራት ወረዳዎች እየተተገበረ ይገኛል ፡፡

በወንቃ ቀበሌም ከእንሰት የተዘጋጁ ቂጣ፣ ኩኪስ ፤ ዳቦቆሎ፣ ቡላና የመሳሰሉት ምርቶች የቀመሳና ምልከታ መረሐ ግብር የቀበሌው አርሶ አደሮች፣ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ ከልማት ባንክ የመጡ ባለሙያዎች እና በእንሰት የምግብ ዝግጅት ላይ የተሳተፉ የቀበሌው ወጣቶች በተገኙበት ተካሄዷል፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is enset2.jpg

በመረሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ.ር ታፈረ መላኩ እንደገለጹት እንሰትን ለምግብነት መጠቀም የተጀመረው በጥንት አባቶቻችን እንደሆነ መረጃዎች ቢያሳዩም ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን እንሰትን ማህበረሰቡ ለምግብነት ሳይጠቀምበት ቆይቷል፡፡ ማህበረሰባችን ሰፋፊ የእርሻ መሬት ባለቤት ቢሆንም የተመጣጠነ ምግብ ባለመጠቀሙ ለረሃብና ለመቀንጨር ተጋልጧል፡፡ በመሆኑም በአካባቢው በጓሮው እንሰትን በመትከል ለምግብነት መጠቀም ይኖርበታል፡፡ በሌላ በኩል ከእንሰት የሚገኘውን ምርት ከራስ ፍጆታ አልፎ ወደ ገበያ በማውጣት ተጨማሪ ሀብት ማፍራትም ይጠበቅበታል ሲሉ አሳስበዋል ፡፡ በየአካባቢው ከተለያዩ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ተመርቀው ለተቀመጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶች በእንሰት ስራ ላይ ቢሰማሩ ተጨማሪ ሀብት ማፍራት እንደሚቻል ይህ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is enset3.jpg

የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር ሀይማኖት ረታ እንደገለጹት እንሰትን ለምግብነት ለመጠቀም በአማራ ክልል በ8 ወረዳዎች በ32 ቀበሌዎች ለመስራት ዕቅድ ቢያዝም አሁን ላይ በ3 ወረዳዎች ብቻ እየተተገበረ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ እንሰት ለቂጣ ፣ለገንፎ፣ ለኩኪስ ፣ ለዳቦ ቆሎ፣ ለአጥሚት፣ ለቃጫ፣ ለአረቄ፣ ለአፈር ማዳበሪያነት እንዲሁም ለእንስሳት መኖነት እንደሚያገልግል የገለፁት ዶ.ር ሃይማኖት እስካሁን ማህበረሰቡ ሳይጠቀምበት መቆየቱንም ተቅሰዉ ከዚህ በኋላ እንሰትን በጓሮው በመትከል የተመጣጠነ ምግበ መመገብና ወደ ገበያ በማውጣት ተጨማሪ ሀብት ማግኘት እንደሚችሉም ተናግረዋል፡፡

የእንሰት ምርትን ለማስፋፍት ከ70 ሺ በለይ የእንሰት ችግኝ በማዘጋጀት ለአካባቢው አርሶ አደሮች ለማከፋፈል በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልፀው በዚህ ላይ ወጣቶች በንቃት በመሳተፍ የራሳቸውን ሀብት እንዲፈጥሩ ለሌሎች የአካባቢው አርሶ አደሮችም የእንሰት አምባሳደር በመሆን እንዲያስተምሩ ሲሉ አሳስበዋል፡፡ በጎዛምን ወረዳ በተመረጡ ት/ቤቶች እና በገዳም ለሚኖሩ መነኮሳት እንሰትን እንዴት ለምግብነት እንደሚዘጋጅ ለማስተማር ዕቅድ መያዙንም ገልፀዋል፡፡

በእንሰት የምግብ ቀመሳ መረሐ ግብር ላይ ተገኝተው ሀሳባቸውን የሰጡት አርሶ አደሮችም እንደገለጹት እስከ አሁን የእንሰት ምርትን በጓሯችን በአካባቢያችን ቢኖርም ለእንስሳት መኖነት ሲጠቀሙበት እንደቆዩና አሁን ግን የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ልማት ጋር በመተባበር ለምግብነት ለማዋል ባደረገው የእንሰት ምገባ ቀመሳ መረሐ ግብር ላይ ተገኝተን ቀመሳ በማካሄዳችንና በመሳተፋችን ተደስተናል፤ የቀመስነው የእንሰት ምግብም ጣፋጭነቱ በጣም ጥሩ ነው፤ እስካሁንም እንሰት ለምግብነት መዋሉን ባለመረዳታችንና ባለመጠቀማችን ተፀጽተናል ሲሉ ሀሳባቸውን በቁጭት ገልፀዋል፡፡

የእንሰትን ተከል በሰፊው በጓሮ በመትከል ለምግብነት ለመጠቀም ዝግጁ እንደሆኑና ወደ ገበያ በማውጣት ተጨማሪ ሀብት ለማግኘት ዕቅድ እንዳላቸው፤ ይህንንም ለማሳካት ዩኒቨርሲቲው የእንሰት መስሪያ ቁሳቂሶችን ድጋፍ ቢያደርግልን ከእኛ አልፎ ለክልላችን ብሎም ለሀገራችን የእንሰትን ምርት ወደ ገበያ ለማቅረብ ፍላጎት አለን ሲሉም ሃሳባቸውን ገልፀዋል፡፡

 


  • -

Li4LaM Project

 

ERASMUS+ is a European Union funding program in the fields of education, training, youth and sport. The program focuses on quality education and intercultural understanding (https://ec.europa.eu/info/funding-tenders/opportunities/portal/screen/home). Land Information for Land Management (Li4LaM) is a project in the thematic area of the capacity building grant of ERASMUS+ program.

Li4LaM is a three years project prepared and to be executed by the consortium effort of eight universities (four from Europe and four from Ethiopia). These Universities are Debre Markos University (DMU), Bahir Dar University (BDU), Weldia University (WU) and Addis Abeba University (AAU) from Ethiopia; and University of Natural Resources and Life Sciences (BOKU) and Technical University of Vienna (TUW) in Austria; University of Agriculture in Krakow (UAK), Poland; and University of Ljubljana (UL), Slovenia.

The Li4LaM project proposal was designed in line with the primary focus area of the funding agency and accordingly the proposal is accepted for funding starting 2023. This project focuses on the following work packages: Elaboration of conceptual framework for modules; capacity building; elaboration of teaching materials; materials purchase and supply; pilots and roll-out of courses; lifelong learning; and quality assurance evaluation.

The University is grateful to the European Union funding agency in general and ERASMUS+ programme in particular for accepting our project proposal for funding. We are also thankful to all the institutions who participated in preparing this winning project proposal with special thanks to the institute of land administration at DMU, Geomatic institute at BOKU and the research group of Geoinformation at TUW. The success of the grant can be evaluated by the great commitment to execute the work packages and achieving targeted deliverables. Accordingly the university wants to describe its commitment for the successful implementation of the project.

NB., To see details about the networking of the institute of land administration, please visit the institute website at http://www.dmu.edu.et/la/

This image has an empty alt attribute; its file name is ERASMUS-logo.png


  • -

የሸበል በረንታ የተቀናጀ የአቅም ማጎልበቻ ልማት ፕሮጀክት የማስጀመሪያ ዓውደ ጥናት ተካሄደ

 

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ እና አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ በትብብር የሚያከናዉኑት የሸበል በረንታ የተቀናጀ የአቅም ማጎልበትና የልማት ፕሮጀክት የሚል የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ፤ የዞኑንና የወረዳዉ ከፍተኛ አመራሮች፤ የክልሉ የገንዘብ ቢሮ እና በየደረጃዉ ያሉ የማህበረሰቡ ተወካዮች በተገኙበት ሸበል በረንታ ወረዳ የዕድዉሃ ከተማ ተካሄደ፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is %E1%88%B8%E1%89%A0%E1%88%8D2.jpg

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት  አቶ ዉብሸት ዳምጤ የሸበል በረንታ ዋና አስተዳዳሪ ሲሆኑ በንግገራቸዉም ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ በወረዳችን ላይ  ያለዉን የመገዳደል (የደም መመላለስ) ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ለማስወገድ በማሰብ የእርቅ ማድ ፕሮግራም እንዲተገበር በማድረግ ወደ አርባ ያህል ግጭቶችን  በአንድ አመት ወስጥ እንዲፈቱ  አስተዋጾ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ አሁን ደግሞ ከአግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመስራት ፕሮጀክት በመቅረጽ በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውንም ጨምረው ተናግረዋል ፡፡

አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ ሸበል በረንታ ወረዳ ከገባ ጊዜ ጀምሮ ለአካባቢዉ ማህበረሰብ አለኝታ ሆኗል፡፡ በተለይ በተፈጥሮ ሀብት ልማት ላይ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ በሰብል ልማት ስራ ላይ ዘለቄታዊነት እንዲኖረዉ በማሰብ ፍኖተ በላይ የራስ አገዝ የህብረት ስራ ማህበርን አቋቁሞ ወደ ስራ ግብቷል፡፡ የህብረተሰቡን አንኳር የሆነውን የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ ፕሮጀክት በመቅረፅ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ 

ከወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ በርካታ ስራዎችን ለአብነትም ፦ እንስሳት ማድለብ፣ ደሮ እርባታ፣ ፍየል እርባታ ናቸዉ፡፡ ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶችን በመታገል እና በወረዳዉ እንዲቀንስ በማድረግ የራሱን ሚና ተወጥቷል፡፡ አሁን ደግሞ በአዲስ ራዕይና መንፈስ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ይህንን ፕሮጀክት ቀርፀዉ  ወደ ስራ ለመግባት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ነዉ በማለት  ፕሮግራሙን በይፋ አስጀምረዋል፡፡

This image has an empty alt attribute; its file name is %E1%88%B8%E1%89%A0%E1%88%8D3.jpg

አቶ ተመስገን ወንድይፍራዉ የአግሪ አርቪስ ኢትዮጵያ የሸበልና የሁለት እጁ ፕሮጀክት ማናጀር  የሸበል የተቀናጀ የአቅም ማጎልበት የልማት ፕሮጀክት  ላይ አጭር ገለጻ  ያደረጉ ሲሆን በገለጻቸዉም  ፕሮጀክቱ ዓለማ ምን ይመስላል፣ ፕሮጀክቱ ያጋጠሙት ችግሮች፣ አፈጻፀም እና የአተገባበር ስልቶች፣ተጠቃሚዎች እነማን ናቸዉ፣ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ስለአደረጉት ስምምነት፣ ከወረዳዉና ከማህበረሰቡ ምን ይጠበቃል?  የሚሉ ነጥቦችን ትኩረት አድርገዉ አጠር ያለ ገለጻ አድርገዋል፡፡

አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ ወደ ጎጃም አካባቢ ከመጣ ወደ 30 አመት አካባቢ እንደሆነውና ወደ ሸበል በረንታ ወረዳ ከገባ ደግሞ 6  አመት እንደሆነዉ በመግለፅ አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ  በዋናነት ትኩረት አድርጎ የሚያከናዉናቸዉ ተግባራት በምግብ ዋስትና፣ አየር ንብረትና ተፈጥሮ ሃብት ልማት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የገቢያ ትስስር፤ አቅም ማጎልበትና የህብረት ስራ ልማት ማህበራትን ማቋቋም ላይ እንደሆነ ገልፀዋል።

ይህ ፕሮጀክት የ 3 አመት ፕሮጀክት ሲሆን  በዘጠኝ ቀበሌዎች እንደሚተገበርም አንስተው  5700  የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ እና 31.8 ሚሊዮን ብር ወጭ እንደሚጠይቅም አብራርተዋል፡፡

የፕሮጀክቱ ዓላማዎችም 350 ሄክታር የተራረቆጠ አካባቢን መልሶ እንዲያገግም ማድረግ፤ ፍኖተ በላይ የራስ አገዝ የልማት ማህበርን ራስ ማስቻል፤ የልማት ተሳትፎን በዘላቂነት ማረጋገጥ ለአሁኑና ለመጭዉ ትውልዶች ምቹ አካባቢን መፍጠር መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በቀረበው ፕሮጀክት እና አተገባበሩ ዙሪያ ወይይት የተደረገ ሲሆን  በዉይይቱም  የተነሱ ነጥቦች መካከል ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ እና አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ በሸበል በረንታ ወረዳ እየሰሩ ያሉት ስራ የሚበረታታ እንደሆነ ተገልጿል።

This image has an empty alt attribute; its file name is %E1%88%B8%E1%89%A0%E1%88%8D4.jpg

ዶ/ር አስካለማሪያም አዳሙ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዘዳንት በበኩላቸው ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት ላይ ትኩረት ሰጦ እየሰራ መሆኑን ገልጸው  ለዚህም ብቁ አመራር እየሰጡ ያሉትን  የዩኒቨርስቲያችንን ፕሬዘዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩን አመስግነዋል፡፡ ለወደፊትም ከመማር ማስተማር እና ችግር ፈች ጥናትና ምርምሮች ከማድረግ ጎን ለጎን የማህበረሰብ አገልግሎትን አጠናክሮ  እንደሚቀጥል  አርጋግጠዋል፡፡

አቶ አበበ መኮንን የም/ስ/ጎ/ዞን ግብርና መምሪያ ም/ኃላፊ እንደተናገሩት ደግሞ ም/ስ/ጎ/ዞን እንደ ሀገር ትርፍማ አምራች አካባቢ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ትርፍ አምራችነቱ ግን እየተጠቀመ እንዳልሆነ ተናግረዋል። የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች (Overlap) እንዲያደረጉ ክትትል እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡

 

This image has an empty alt attribute; its file name is %E1%88%B8%E1%89%A0%E1%88%8D5-1.jpg

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩ በዉይይቱ ማጠቃለያና መዝጊያ ንግራራቸዉ እንደተናገሩት  ከተረጅነት በመወጣት እራሳችንን መቻል እንደሚገባ፣   የወረዳዉ ማህበረሰብ ጠንክሮ በመስራት እራሱን መለወጥ እንደሚገባው፤ በፕሮጀክቱ የሚታቀፉ ሰዎችን በአግባቡ መምረጥ እንደሚገባና ፕሮጀክቱ ሁለገብ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

የሚሰሩ ፕሮጀክቶችም ጥራታቸዉን የጠበቁ እንዲሆኑ የፕሮጀክት ትግበራ ዲስፒሊን በመከተል ሂደቱን በየጊዜዉ መገምገም እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

በመጨረሻም የዕድ ዉሃ ከተማ ላይ አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ ያለማውን የቦረቦር መሬት ጉብኝት ተደርጎ መርሃ ግበሩ ተፈፅሟል፡፡


Search DMU

Upcoming Events

There are no upcoming events.

Partners

DMU Radio Broadcasting . . .