GROW WISER AT THE WATER TOWER
Staff Academic Administrative Graduate
ቀን 21/10/2013
ማስታወቂያ
ለአዲስ የ2ኛ ዲግሪ የማታ (extension) ፕሮግራም የግል ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ፡-
ቀደም ሲል የደ/ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ድህረ ምረቃ ኮሌጅ በቀን 27/9/2013 ዓ.ም በማስተርስ/Masters/ ዲግሪ በልዩ ልዩ የትምህርት መስኮች አመልካቾችን በማታው ወይም በኤክስቴንሽን ትምህርት ፕሮግራም ተቀብሎ ለማስተማር የምዝገባ ጊዜና የፈተና ቀን በመግለጽ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡
ይሁንና የተሰጠው የምዝገባ ጊዜ በቂ አለመሆኑን በመጠቆም ጊዜው እንዲራዘም ከአመልካቾች በቀረበው ጥያቄ መሰረት ከግንቦት 30/9/2013 እስከ ሰኔ 24/10/2013 ዓ.ም የነበረው የመመዝገቢያ ቀን እስከ ሃምሌ 8/11/2013 ዓ.ም የተራዘመ ሲሆን የመግቢያ ፈተና መስጫ ቀን ደግሞ ሃምሌ 10-11/2013 ዓ.ም መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
ድህረ ምረቃ ኮሌጅ
There are no upcoming events.
DMU Radio Broadcasting . . .